በብዛት የተነበቡ መጣጥፎች

መደብ

ቤተ-ክርስቲያን

መሪ ፓስተር ከመሆንዎ በፊት መጠየቅ ያለብዎት አስፈላጊ ጥያቄዎች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ጆሴፍ ማቴራ : ሁላችንም እንደምናውቀው በሺዎች የሚቆጠሩ መሪ ፓስተሮች በየ ዓመቱ የሙሉ ጊዜ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎትን ለቀው። ይወጣሉ፡፡ በእነዚያ ተመሳሳይ ግዜዎች ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ የቤተክርስቲያን ግንባታዎች ከሦስት ዓመታት በላይ አልፈው አያውቁምⵆ አንደኛው ምክንያት አብዛኛዎቹ መሪ ፓስተሮች ራሳቸውን የሚከተሉትን ጥያቄዎች በሐቀኝነት ስለማይጠይቁ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ የመሪነት ሚናውን ለመወጣት የሚያስችለኝን ሚና ለመውሰድ ስሜታዊ ብስለት አለኝ? […]

READ MORE

ዛሬ ተሐድሶን ለመመልከት ለምን ተሳነን

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዳንኤል ኬ. ኖሪስ : ታህሳስ 7 1941 ፤ ጃፓን ፐርል ሃርበር በሚባል ቦታ አሜሪካ ላይ ያልተጠበቀ ጥቃት አድርሳ ነበር ።ይህ በፓሲፊኩ የጦር ክፍል ላይ በደረሰው ጥቃት ሀገራችን 2403 ዜጎቻን አጣች።በቀጣዩ ቀን ፕሬዝዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት ጥቃቱ በአሰቃቂነቱ እና አሳፋሪነቱ የሚታወስ ነው ሲሉ ለሀገሪቱ ተናገሩ። ያም ጥቃት አሜሪካ 4 አመት ለቆየ እና 400,000 ዜጎቿን ላሳጣት አለምአቀፋዊ ግጭት ውስጥ […]

READ MORE

በዚህ ዘመን ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ 3 ስህተቶች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

በርት ኤም. ፋሪስ : በቅርቡ አንድ የቴሌቪዥን ሰባኪ እንዲህ ሲል ሰማሁት “እግዚአብሔር አሜሪካ ላይ የሚፈርድ ከሆነ ኢየሱስን ይቅርታ መጠየቅ ይኖርበታል።” ነገር ግን ቃሉ እንዲህ ነው የሚለው፥ “የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው።” (1 ጴጥሮስ 3:12). “ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል።” (2 ጴጥሮስ 2:9). በዚህ ዘመን ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚታየው የመጀመሪያው ስህተት የእግዚአብሔርን ፍርድ እና ቁጣ በተመለከተ ያለው ቸልተኝነት ነው።   የእግዚአብሔርን ፍርድ አለመረዳት የጠቀስኩት ሰባኪ መረዳቱ ሚዛናዊነት እና የእግዚአብሔር […]

READ MORE

መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ያሉ ብልሹ እሴቶችን ማስወገድ ይፈልጋል

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

በርት ኤም. ፋርያስ : በ 2002 ረዘም ባለ የ ጾም እና የጸሎት ጊዜ ዉስጥ በነበርኩበት ወቅት ከእኔ በላይ ከመስታወት የተሰራ ጣራ አይ ነበር፤ በአገልግሎቴ የምፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ ሞገስ፣ ቅባት፣ ሃይል፣ የተከፈቱ በሮች፣ ተጽዕኖ እና ሌሎችም ከሌላኛው በኩል ነበሩ። ነገር ግን እኔ ጣራ ጣራውን ሳይ እግዚአብሔር አምላክ ወደታች እንዳይ እያመለከተኝ ስለቆምኩበት መሰረት እና ስለ ባህሪዬ ይናገረኝ ነበር። በወቅቱ ጽፌው […]

READ MORE

21 በትንቢት ማነፅ እና በማታለል መካከል ያሉ ንጽጽሮች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶ/ር ጆሴፍ ማቴራ : መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እውነተኛ ትንቢት ቤተክርስቲያንን ያንፃል እንዲሁም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከፍ ከፍ ያደርጋል (1 ቆሮ 12፡3-7 እና 14፡3-4)። ይሁን እንጂ፣ እውነተኛ የትንቢት ስጦታ ባለበት ሁኔታ፣ የትንቢት ጸጋን ትክክል ባልሆነ መንገድ የሚጠቀሙ አይጠፉም። ለምሳሌ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነብዩ በለዓም የተሰጠውን ስጦታ ለገንዘብ ብልጽግና ሊጠቀም ሲሞክር እናያለን (ዝኁ 22፡21-39)። በዚህ የበለዓም ትረካ ውስጥ፣ ምንም እንኳ አላማው መልካም ባይሆንም፣ በለዓም ቦና ፊዴ (እውነተኛ) […]

READ MORE

7 ኢየሱስ በመጨረሻ ትምህርቱ ላይ ያስተማራቸው ጠንካራ ነጥቦች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ሮን አለን : ኢየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ለእያንዳንዷ እስትንፋስ በከፍተኛ ስቃይ እየታገል ሣለ፣ እርሱ ማን እንደነበረ እና በወቅቱ ምን እየሆነ እንዳለ የሚያሳዩ ሰባት አጫጭርና ኃይለኛ ንግግር ተናገረ። እርሱንም በነዚህ ቃላት፣ እርሱን የሚከተሉን ሰዎችን በሙሉ ያበረታታል። ይህ የእርሱ የመጨረሻ ስብከት ነበር። “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” (ሉቃ 23:34) ኢየሱስ በሄደበት ለሰዎች ይቅርታን በመስጠት ብቻ ሳይሆን በመስበክም አገልግሏል (ማቴ 5፡44)፣ ለሃጥያት ይቅርታ በማድረግ መለኮታዊ ጌታ መሆኑን አውጇል (መዝ […]

READ MORE

3 ኢየሱስ እንደ ሊቀ-ካህንነቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ጀንቲዘን ፍራንክሊን : የኣካል ብቃት የ27 ቢልየን ዶላር ኢንደስትሪ ነው። በየ ዓመቱ መስከረም ሲጠባ በሰውነት ማጎልመሻ ቤቶች አባል የሚሆኑ ሰዎች ብዛት በእጅጉ ይጨምራል። ነገር ግን አባል ሆነው አካላቸውን ለማብቃት ከተቀላቀሉት መካከል 80% ያክል የሚሆኑት ጥቅምት በገባ በሁለተኛ ሳምንቱ ቁርጥ አድርገው ያቆማሉ። ብዙዎቻችን ብቁ ሆኖ የመታየትን ሃሳብ እንወደዋለን፣ ነገር ግን በተጨባጭ ብቁ ለመሆን የሚጠይቀው ቆራጥነት ይጎድለናል። በ ዘሌ 16፡21፣ እግዚአብሔር ብቁ […]

READ MORE

የተበረዘ፣ ምቾት የሚሰጥ፣ እና አለማዊ የሆነን ወንጌል ስለምን ወደድን?

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ሼን ፊልፖት : ዮሴፍ የሁለተኛ ልጁን ስም ኤፍሬም ብሎ ነበር የጠራው እንዲህ ሲል ፦ “እግዚአብሔር በመከራዬ አገር ፍሬአማ አደረገኝ”።(ዘፍ 41 ፡ 52) ዮሴፍ የቀረዉን ሕይወቱን የኖረው መከራን በተቀበለበት ምድር ነበር።”መከራ” ትርጉሙ ብዙ ነው፤ ስቃይ፣ ችግር፣ ሸክም፣ እና ፈተና ማለት ነው።  ህመም እና አደጋ ማለት ነው። በጭንቅ የተሞላ ማለትም ነው። ይህ “የመከራ አገር” ዮሴፍ እግዚአብሔርን እና ህዝቡን ያገለገለበት ነው፤ እግዚአብሔር ወደዚህ አገር […]

READ MORE

ክርስቲያኖች ምልካም ላልሆነ ባህሪያቸው እ/ርን ተጠያቂ ለማድረግ የሚጠቀሙባቸው 5 ተጭማሪ መንገዶች (ክፍል 2)

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶክተር ጆሴፍ ማቴራ : ኢየሱስ በአስገራሚ ሁኔታ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ልምምዶችን የእግዚአብሔርን ቃል በመጥቀስ የሚያደርጉ ሰዎች ያጋጥሙት ነበር። ይህንንም በጊዜው የነበሩት የአይሁድ መሪዎች በማርቆስ ወንጌል 7 ፥ 9 – 13 እናትን እና አባትን መርዳትን በቁርባን መስዋእት ሲቀይሩ ተገልጦ እናየለን። መጽሃፍ ቅዱሳችንን ስናጠና ሰይጣንም እራሱ የእግዚአብሔርን ቃል እንደሚያውቅ እና ለራሱ እንደሚመቸው ሲጠቅስም እናያልን። (ሉቃስ 4፥9 – 12)።በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዳለ አንድ […]

READ MORE

ክርስቲያኖች ምልካም ላልሆነ ባህሪያቸው እግዚአብሔርን ተጠያቂ ለማድረግ የሚጠቀሙባቸው 5 መንገዶች (ክፍል 1)

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶክተር ጆሴፍ ማቴራ : ኢየሱስ በአስገራሚ ሁኔታ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ልምምዶችን የእግዚአብሔርን ቃል በመጥቀስ የሚያደርጉ ሰዎች ያጋጥሙት ነበር። ይህንንም በጊዜው የነበሩት የአይሁድ መሪዎች በማርቆስ ወንጌል 7 ፥ 9 – 13 እናትን እና አባትን መርዳትን በቁርባን መስዋእት ሲቀይሩ ተገልጦ እናየለን። መጽሃፍ ቅዱሳችንን ስናጠና ሰይጣንም እራሱ የእግዚአብሔርን ቃል እንደሚያውቅ እና ለራሱ እንደሚመቸው ሲጠቅስም እናያልን። (ሉቃስ 4፥9 – 12)። በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዳለ አንድ ታዛቢ […]

READ MORE

ማሕደር

Language
WordPress Image Lightbox