በብዛት የተነበቡ መጣጥፎች

ጸሐፊ

toledit

ጠላት የትንቢት ቃላችንን ሲያጠቃ ምን መደረግ አለበት

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ካቲ ዴግራ : ከሶስት አመት በፊት፣ የነበሩኝ አብዛኛዎቹ ትንቢታዊ መልዕክቶች ተፈጽመው አልፈዋል። የእግዚአብሔር መንግስት ይስፋፋና የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም በክብር ይልቅ ዘንድ፣ ጌታ ተጨማሪ የትንቢት መልዕክቶችን በህይወቴ እንዲያመጣ በጸሎት እጠይቀው ነበር። በቅዱስ ቃሉ እንደተጻፈው፤ “ከእውቀት ከፍለን እናውቃለንና፥ ከትንቢትም ከፍለን እንናገራለንና” (1 ቆሮ 13:9)። ትንቢት ድርሻ ነው። የመጀመሪያው ድርሻ የትንቢት ተናጋሪ ሰው፣ የመልዕክትን ቃል ማድረስ ሲሆን፤ ሁለተኛው ድርሻ ደግሞ የእኛ በጸሎት፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመተባበር፣ የትንቢት ቃሉን ትርጉም መረዳት የሚያስችለንን ጸጋ በመቀበል በነፃነት እንዲገለጥ መፍቀድ ነው። ለምሳሌ ባለጠጋ እንደምንሆን የትንቢት ቃልን ብንቀበል፣ በዝምታ ቁጭ ብለን 1ሚልየን ብር ከሰማይ እንዲወርድ ወይንም ደግሞ የሆነ ሰው ትልቅ መጠን ያለው ቼክ እንዲጽፍልን መጠበቅ የለብንም። ይልቁንስ መንፈስ ቅዱስ አዳዲስ የፈጠራ ሃሳቦችን፣ የቢዝነስ ስልትንና አዳዲስ ግኝቶችን እንዲያሳየን እርሱን በጸሎት መቅረብና መጠየቅ ይኖርብናል። ብዙውን ጊዜ ባለጸጎች የምንሆነው ጌታ እንዲኖረን በፈቀደው ሃብት ለመባረክ የሚያስችለንን መንገድ እንዲያሳየን እርሱን በመፈለግ ላይ ሳለን ነው። የትንቢት ቃሉ መወራት ሲጀምር ጦርነት ይነሳል። ቃሉ በመንፈሳዊው አለም እንደተለቀቀ፣ ተቃዋሚው እና አበሮቹ በህይወታቹ በተነገረው ትንቢት ላይ አመጻን ለማወጅ መሞካራቸው አይቀሬ ነው። ስለዚህ እኛም በተቃርኖ፣ ጦርነትን በማወጅ መቃወምና የሚመጣውን መልዕክት ለማጥቃት የሚንቀሳቀሰውን ሁሉ በስልጣን መቆጣጠር ይገባናል። ቃሉንም በኃይል መቀበል አለብን! “መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፥ ግፈኞችም ይናጠቋታል” (ማቴ 11:12)። በዘመናዊው የኢንግልዘኛ ትጉርም “መንግሥተ ሰማያት በኃይል ተስፋፍታለች፥ በኃይልም ብርቱዎች ይናጠቋታል”  ይላል። እኛ ታድያ ብርቱዎች በመሆን ያን የተመኘነውን ነገር በኃይል፣ በጸሎት፣ በማወጅና በኢየሱስ ክርስቶስ ባገኘነው ስልጣን መቀበል ይኖርብናል። ኢየሱስ እና አብ በነገሮች ላይ ስልጣንን በመውሰድ ለመፍጠርና ህያው ለማድረግ ተናገሩ (Speak Out, የሚለውን መፅሐፌን ተመልከቱ)። ድምፃችንን በማሰማት መፀለይና ቃልን በማውጣት መናገር አለብን። ኢየሱስ ሥልጣን ሰጥቶናል፣ እናም ድምጻችንን በማሰማት በመጸለይ እና የትንቢት ቃላችንን ወደ መገለጥ እንዲመጡ በመናገር ይህንን ስልጣን መቀበል ያስፈልገናል። ያለ ምንም ተግባር በዝምታ ተቀምጠን ነገሮች በታዕምር እንዲገለጡና […]

READ MORE

21 በትንቢት ማነፅ እና በማታለል መካከል ያሉ ንጽጽሮች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶ/ር ጆሴፍ ማቴራ : መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን እውነተኛ ትንቢት ቤተክርስቲያንን ያንፃል እንዲሁም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ከፍ ከፍ ያደርጋል (1 ቆሮ 12፡3-7 እና 14፡3-4)። ይሁን እንጂ፣ እውነተኛ የትንቢት ስጦታ ባለበት ሁኔታ፣ የትንቢት ጸጋን ትክክል ባልሆነ መንገድ የሚጠቀሙ አይጠፉም። ለምሳሌ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነብዩ በለዓም የተሰጠውን ስጦታ ለገንዘብ ብልጽግና ሊጠቀም ሲሞክር እናያለን (ዝኁ 22፡21-39)። በዚህ የበለዓም ትረካ ውስጥ፣ ምንም እንኳ አላማው መልካም ባይሆንም፣ በለዓም ቦና ፊዴ (እውነተኛ) […]

READ MORE

7 ኢየሱስ በመጨረሻ ትምህርቱ ላይ ያስተማራቸው ጠንካራ ነጥቦች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ሮን አለን : ኢየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ለእያንዳንዷ እስትንፋስ በከፍተኛ ስቃይ እየታገል ሣለ፣ እርሱ ማን እንደነበረ እና በወቅቱ ምን እየሆነ እንዳለ የሚያሳዩ ሰባት አጫጭርና ኃይለኛ ንግግር ተናገረ። እርሱንም በነዚህ ቃላት፣ እርሱን የሚከተሉን ሰዎችን በሙሉ ያበረታታል። ይህ የእርሱ የመጨረሻ ስብከት ነበር። “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” (ሉቃ 23:34) ኢየሱስ በሄደበት ለሰዎች ይቅርታን በመስጠት ብቻ ሳይሆን በመስበክም አገልግሏል (ማቴ 5፡44)፣ ለሃጥያት ይቅርታ በማድረግ መለኮታዊ ጌታ መሆኑን አውጇል (መዝ […]

READ MORE

3 ኢየሱስ እንደ ሊቀ-ካህንነቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ጀንቲዘን ፍራንክሊን : የኣካል ብቃት የ27 ቢልየን ዶላር ኢንደስትሪ ነው። በየ ዓመቱ መስከረም ሲጠባ በሰውነት ማጎልመሻ ቤቶች አባል የሚሆኑ ሰዎች ብዛት በእጅጉ ይጨምራል። ነገር ግን አባል ሆነው አካላቸውን ለማብቃት ከተቀላቀሉት መካከል 80% ያክል የሚሆኑት ጥቅምት በገባ በሁለተኛ ሳምንቱ ቁርጥ አድርገው ያቆማሉ። ብዙዎቻችን ብቁ ሆኖ የመታየትን ሃሳብ እንወደዋለን፣ ነገር ግን በተጨባጭ ብቁ ለመሆን የሚጠይቀው ቆራጥነት ይጎድለናል። በ ዘሌ 16፡21፣ እግዚአብሔር ብቁ […]

READ MORE

አለማችሁን እስከዘለቄታው የሚቀይሩ አምስት የትንሳኤ ቱርፋቶች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶክተር ኤዲ ሂያት : በካናዳ አገር በሚገኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ውስጥ በመነቃቃት ዙሪያ አንድ ሳምንት የሚፈጅ ትምህርት በማስተምርበት ወቅት አንድ ቀን ከ ለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ራሴን ነቅቼ አገኘሁት። በአእምሮዬ በክርስቶስ ትንሳኤ ሰይጣን ላይ የድረሰበትን ፍጹም የሆነ ሽንፈት እያሰላሰልኩ ነበር፤ ይህንንም እውነት የዛኑ ቀን ጠዋት ክፍል ውስጥ ማካፈል እንዳለብኝ ተሰማኝ። ብዙዎች ሰይጣንን አጉልቶ በሚያሳይ እና የእግዚአብሔርን […]

READ MORE

የተበረዘ፣ ምቾት የሚሰጥ፣ እና አለማዊ የሆነን ወንጌል ስለምን ወደድን?

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ሼን ፊልፖት : ዮሴፍ የሁለተኛ ልጁን ስም ኤፍሬም ብሎ ነበር የጠራው እንዲህ ሲል ፦ “እግዚአብሔር በመከራዬ አገር ፍሬአማ አደረገኝ”።(ዘፍ 41 ፡ 52) ዮሴፍ የቀረዉን ሕይወቱን የኖረው መከራን በተቀበለበት ምድር ነበር።”መከራ” ትርጉሙ ብዙ ነው፤ ስቃይ፣ ችግር፣ ሸክም፣ እና ፈተና ማለት ነው።  ህመም እና አደጋ ማለት ነው። በጭንቅ የተሞላ ማለትም ነው። ይህ “የመከራ አገር” ዮሴፍ እግዚአብሔርን እና ህዝቡን ያገለገለበት ነው፤ እግዚአብሔር ወደዚህ አገር […]

READ MORE

ተሐድሶ ሲሳሳት

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ኤዲ ሃያት : መንፈስ-መር ተሐድሶ(መነቃቃት) ወደ ሥጋዊ ስሜት ሲለወጥ እንዴት እናውቃለን? ለእኔ፣ አንድ ለመስበክ ዕቅድ በተያዘልኝ ሞቅ ባለ “የተሐድሶ” ቤተ-ክርስቲያን ዉስጥ ተከሰተ፤ በምስጋና እና በአምልኮ አገልግሎት ጊዜ፣ ሰዎች በፈንጠዝያ ስሜት እየጮኹ፣ ባንዲራዎችን እያውለበለቡ እና በመተላለፊያዎች ላይ እየሮጡ ነበር፤ እኔ ግን በጸጥታ እያመልክሁ ሳለ መንፈስ ቅዱስ ሲናገር፤ “የማታለል ምሽጉ ኩራት ነው” ሲል ሰማሁ። ወድያውኑ ለጉባዔው ማስተላለፍ የነበረብኝን ሀሳብ ተረዳው። እርሱም፣ በመንፈሳዊ የተሐድሶ ወቅት ኩራት እንዴት ሾልኮ እደሚገባ፤ ምክንያቱ ደግሞ ከእግዚአብሔር ሀይል እና በረከት የተነሣ እንደሆነ ነው። ግለሰቦች እና አብያተ-ክርስቲያናት በህይወታቸው በተገለጠው በእግዚአብሔር ባርኮት ምክንያት የራሳቸውን የተለጠጠ የበላይነት ሃሳብና ምስል ይጨብጣሉ። ይህ ኩራት የኋላ […]

READ MORE

ክርስቲያኖች ምልካም ላልሆነ ባህሪያቸው እ/ርን ተጠያቂ ለማድረግ የሚጠቀሙባቸው 5 ተጭማሪ መንገዶች (ክፍል 2)

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶክተር ጆሴፍ ማቴራ : ኢየሱስ በአስገራሚ ሁኔታ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ልምምዶችን የእግዚአብሔርን ቃል በመጥቀስ የሚያደርጉ ሰዎች ያጋጥሙት ነበር። ይህንንም በጊዜው የነበሩት የአይሁድ መሪዎች በማርቆስ ወንጌል 7 ፥ 9 – 13 እናትን እና አባትን መርዳትን በቁርባን መስዋእት ሲቀይሩ ተገልጦ እናየለን። መጽሃፍ ቅዱሳችንን ስናጠና ሰይጣንም እራሱ የእግዚአብሔርን ቃል እንደሚያውቅ እና ለራሱ እንደሚመቸው ሲጠቅስም እናያልን። (ሉቃስ 4፥9 – 12)።በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዳለ አንድ […]

READ MORE

ክርስቲያኖች ምልካም ላልሆነ ባህሪያቸው እግዚአብሔርን ተጠያቂ ለማድረግ የሚጠቀሙባቸው 5 መንገዶች (ክፍል 1)

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ዶክተር ጆሴፍ ማቴራ : ኢየሱስ በአስገራሚ ሁኔታ መጽሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ልምምዶችን የእግዚአብሔርን ቃል በመጥቀስ የሚያደርጉ ሰዎች ያጋጥሙት ነበር። ይህንንም በጊዜው የነበሩት የአይሁድ መሪዎች በማርቆስ ወንጌል 7 ፥ 9 – 13 እናትን እና አባትን መርዳትን በቁርባን መስዋእት ሲቀይሩ ተገልጦ እናየለን። መጽሃፍ ቅዱሳችንን ስናጠና ሰይጣንም እራሱ የእግዚአብሔርን ቃል እንደሚያውቅ እና ለራሱ እንደሚመቸው ሲጠቅስም እናያልን። (ሉቃስ 4፥9 – 12)። በክርስቶስ አካል ውስጥ እንዳለ አንድ ታዛቢ […]

READ MORE

6 የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን የተሃድሶ ምልክቶች

DATE : November 29, 2019 AUTHOR : COMMENTS : No Comments

ራየን ልስትሬንጅ : እኛ በተሐድሶ ዘመን ውስጥ ነው ያለነው። መንግሥተ ሰማይ በመንግሥቷ የግንባታ እቅዶች የታጠቁ አዳዲስ ግንበኞችን እየላከች ነው። በመንፈሴ እንዲህ የሚል ቃል ሰማሁ፣ “ለተከታዮቼ እና ጸንተው ለሚቀጥሉት አዲስ የህንፃ እቅድ እሰጣቸዋለሁ!” እነዚህ በሰማይ ተልዕኮ ያላቸው ግንበኞች በግንባር ቀደምትነት እንዲጠሩ ከቶ ያላሰቡ ሊሆኑ ይችላሉ። እነዚህም ልክ እንደ ዳዊት በምድረ በዳ የእግዚአብሔርን ክብር የሚፈልጉ እና የሚጠብቁ ሰዎች ይሆናሉ። ነህምያ 2፡18 ላይ የ አሁኗ ቤተ-ክርስቲያን የመነሳት እና የመገንባት ወቅት ላይ ትገኛለች። ይህም ወቅት የሚገለፀው በእነዚህ ስድስት መንገዶች ነው። አዲስ እየወጡ […]

READ MORE

ማሕደር

Language
WordPress Image Lightbox